ሀሳብ አታብዛ ነገ ምን ይሆናል ብለህ አትጨነቅ። ምንም ሀሳብና ጭንቀት ብታበዛ የሚሆነው ነገር መሆኑ አይቀርም።
ትልቅ ስልጣን ትፈልግ ይሆናል።ከሁሉ የሚበልጠው ግን ያለ ሀሳብና ጭንቀት መኖር ነው።
ስለሆነው እንጂ ስለሚሆነው ነገር አትናገር።ሌሎችም ቢነግሩህ አትመናቸው። መልካም ነገር እያደረክ ወደ ፊት የሚሆነውን ጠብቅ።
ሮጠህ ከማታመልጠው ነገር አትሽሽ።
በልተህ ስትጠግብ ርሃብን ሀብታም ስትሆን ድህነትን ስትሾም ሽረትን አትርሳ።
Comments
Post a Comment